ክፍል ሁለት
---------
ይህ ጽሁፍ አፈሩ ይቅለላቸውና እውቁ የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት (Richard Pankhurst ) በታሪክ በኢትዮጵያ ስለተከሰቱ ወረርሽኞች በ linkethiopia.org ላይ The History Of Epidemics በሚል ዐቢይ ርዕስ በሰባት ተከታታይ ክፍሎች ከጻፏቸው ተከታታይ ጽሁፎች ለሰዋሰው ቤተሰቦች እንዲስማማ ወደ አማርኛ ተመልሶ የቀረበ ነው።
የ15ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ፡ አጼ ዘርዓያዕቆብ
---------
በ15ኛው ክፍለ ዘመን የተከሰቱ ወረርሽኞች ከቀደሙት በተሻለ ሁኔታ በታሪክ መዝገብ ተጽፈው የተቀመጡ ናቸው። የመጀመሪያውን ወረርሽኝ የመዘገበው ማቅሪሲ የተባለ ዓረብ ታሪክ ጸሀፊ ነው። ማቅሪሲ እንደዘገበው አጼ ዘርዓያዕቆብ ወደ ስልጣን ማማ እየወጡ በነበረበት ዘመን በ 839 ዓመተ ሂጅራ(1435-1436 ዓ.ም) መላ ሀገሩን ያዳረሰ የበሽታ ወረርሽኝ ተከስቶ ህዝቡን ፈጀው። በግዜው የነበረው ገዢም ሞተ። ይህ ገዢ በስም ባይጠቀስም ምናልባትም ከአጼ ዘርዓያዕቆብ በፊት በድምሩ ለአራት ዓመታት ብቻ ስልጣን ላይ ከነበሩት እንድሪያስ፣ ተክለማሪያም፣ ሰርዌ እየሱስ ወይም አመደ እየሱስ አንዱ ሳይሆን እንዳልቀረ ይገመታል።
ከዘመነ አጼ ዘርዓያዕቆብ እስከ ጎንደር መነሳት
----------
በአጼ ዘርዓያዕቆብ ዜና መዋዕል እንደተጻፈው ከ1454-1468 ዓ.ም. ባሉት ዓመታት ተከታታይ የበሽታ ወረርሽኞች ሲከሰቱ አጼ ዘርዓያዕቆብ አዲስ በቆረቆሯት መናገሻ ከተማቸው ደብረ-ብርሃን ነበሩ። የከተማውም ሰው የሞተን ቀባሪ እስኪጠፋ በወረርሽኙ አለቀ። ንጉሱ ዘርዓያዕቆብም መታሰቢያው በቆመበት ህዝቡን በወረርሽኝ ላይፈጅ ከአምላኩ ቃልኪዳን ባለው ቅዱስ ቂርቆስ ስም ቤተክርስቲያን እንዲገነባ አዘዙ። ተገነባም። ከዚህም ብኋላ የዜና መዋዕሉ ጸሀፊ እንደሚናገረው የንጉሱ እምነተ ጠንካራነት ወረርሽኙን ወደ ቤተ መንግስቱ ክልል እንዳይደርስ አደረገው።
በትረ ሙሴ
---------
ወረርሽኙ ከጠፋ ብኋላ አጼ ዘርዓያዕቆብ የተረፈውን ሰው በአንድ እንዲሰበሰብ አዘዙ። በእጃቸውም በትር እና የዛፍ ቅርንጫፍ እንዲይዙ አደረጉ። ንጉሱም ስብስቡን የወንጌላዊያን ጉባዔ በትሩንም በትረ ሙሴ ሲሉ ሰየሙት። የተሰበሰበውም ሰው በያዘው ቅርንጫፍ ጸበል እያርከፈከፈ የሞተውን ሰው በወጉ ቀበረ።
ሙሉውን ከዋናው የሰዋስው ገፅ ያንብቡ!
https://am.sewasew.com/p/%E1%8B%A8%E1...
ለተጨማሪ ፅሁፎች የሰዋስው መተግበሪያዎችን ያውርዱ ወይም ድረ ገፃችንን ይጎብኙ!
https://sewasew.page.link/ey3j
#ሰዋስው #የወረርሽኝ #ታሪክ #Sewasew #History #Pandemic #Ethiopia #Ethiopian #Richard #Pankhurst #ሪቻርድ #ፓንክረስት