መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል

Опубликовано: 11 Июль 2026
на канале: Muja Mercury
14,830
172

መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል

መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል፡፡

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ የእሳት አደጋዉን በቁጥጥር ስር በማዋል ርብርብ ላደረጉ፤ በርካታ ሎጀስትክ በማቅረብ የደገፉ እና ከዚህ በላይ ሊደርስ የነበረዉን ጉዳት የቀነሱ አካላትን አመስግነዋል፡፡

በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳትና መንስኤዉን በማጣራት ቀጣይ ለህብረተሰቡ የምናሳዉቅ ይሆናልም ብለዋል፡፡

ህብረተሰቡ መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግም አሳስበዋል፡፡