SHILIMATE NEH (ሽልማቴ ነህ) - Intimate Worship (Live)

Опубликовано: 06 Октябрь 2024
на канале: Mesfin Mamo
606,864
3.6k

ኢየሱስ ስጦታ ወይስ ሽልማት?

እያንዳንዱ መዝሙር በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሲመሠረት ብቻ ነው በሰው ሕይወት ላይ ሰማያዊ ተጽእኖ ሊያመጣ የሚችለው። ይህንን መዝሙር የተቀበልኩት በ2001 ዓ.ም እ.ኤ,አ ነበር። መዝሙሩ በፊልጵስዩስ ምእራፍ 3 ላይ የተመሠረተና በሕይወት ተሞክሮዬም የተፈተሸ ነው። ኢየሱስ እንድንበት ዘንድ ከአብ የተሰጠ ስጦታችን ነው (ዩሐንስ 4:10 )።

ኢየሱስ ለአማኝ በተጨማሪም ሽልማቱ ነው

“እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ላይ ስለ ጠራኝ፣ ሽልማት ለመቀዳጀት ወደ ግቡ እፈጥናለሁ።”
‭‭ፊልጵስዩስ‬ ‭3:14‬

የእግዚአብሔር ርስቱ ሕዝቡ፤ የልጆቹም ርስት ደግሞ እግዚአብሔር ነው። (ዘዳግም 18፥2፣ መዝሙር 16፥5) እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ እኛን የሚባርከን በራሱ ነው፡፡ የሚያደርግልን ነገር ሁሉ ከእርሱ አይበልጥምና። በፊልጵስዮስ 3 ላይ የተያዝኩበትን ያን ልይዝ እፈጥናለሁ ሲል የያዘው ጌታ እንደሆነና በሩጫው መጨረሻ ላገኘው የምፈልገው ኢየሱስ ነው ማለቱ ነው። ይህን የሚለው ኢየሱስን ስላላገኘው ሳይሆን ሙላቱን በመጠማት እንደሆነ ያመለክታል። ጌታን ሽልማቴ ነህ ስለው ልቀበል ከምችለው የአገልግሎት ሽልማት በላይ ሽልማቴ በአንተ እቅፍ ለዘላለም መኖርና መጠቅለል ነው እያልኩኝ ነው። በራዕይ 4 ላይ 24ቱ ሽማግሌዎች አክሊላቸውን በዙፋኑ ሥር አድርገው እንደሰገዱለት ማለት ነው። በሙሴ ሕይወት ደግሞ ይህንን እናነባለን፦ "ከግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ፤ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።" ለሙሴ ብድራቱ ወይም ሽልማቱ ምንድን ነበር ብለን ብንጠይቅ ከነዓን አልነበረም፤ ከነዓን አልገባምና። ነበር ግን እርሱ የተጠማው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ነበር። እግዚአብሔር ደግሞ ክብሬን ማየት ስለማትችል በሰንጣቃው አለት ቆመህ ጀርባዬን ታያለህ አለው። ይህም ሙሉ ክብሩን ማየት እንደማይችል እየነገረው ነበር። የእግዚአብሔር ክብር ደግሞ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የሙሴ ጸሎት ሙሉ መልሱን ያገኘው ከ2ሺህ ዓመታት በኋላ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ክርስቶስ ልብሱ ሲያበራ ሙሴና ኤልያስ በአጠገቡ ሲታዩ ነበር። የአንድ መንፈሳዊ ሰው አቻ የሌለው ብድራት ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና።

ከማን ጋር ለመወዳደር ነው የምሮጠው ለሚለው ደግሞ ቃሉ በ1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24 ላይ እንደተጻፈው፦ "በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።" ይላል። የምሮጠውና የምገሰግሰው ሽልማት ሊቀበል እንደሚሮጥ ሯጭ ነው። ይህም በዓላማ፣ በዲሲፕሊን፣ በትጋት፣ በተስፋ፣ በእምነትና በዝግጅት እንደሚወዳደር ሯጭ ማለት ነው። በዕብራውያን 12:1-2 እንዲህ ይላል:- “እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”

SEMAYAWI FILM presents SHILIMATEH NEH by MESFIN MAMO
executive producer NAHUSENAY MAMO, KALEB MAMO, EMMANUEL WORSHIP CENTER director WENDWESEN REGASA production manager ASER SEIFU music arrangement DAWIT GETACHEW sound NISTUH YILMMA band SAMUEL WORKNEH, ROBEL TEFERA background choir BINIYAM YONAS, AMANUEL MUSE, LIDYA ANTENEH, MERON ALEMU (JUDY), NATAN DESTA, HANNAH WETENE, SAMUEL SHIFERAW, FENAN BEFEKADU camera ASER SEIFU (AVA), ABENEZER GIRMA, KALEAB TSEGAYE, MOTI TAINA, FIKR ALEX, EYOB TESFAYE, BASLAEL, TADESSE setting designer TIGIST MESHESHA location manager KULENI BIRHANU editing WENDWESEN REGASA, ABENEZER GIRMA co-ordinator REDIET TEREFE assistant co-ordinator SARA PAULOS